የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዘንድሮው የመኸር እርሻ 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዷል 

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦በዘንድሮው የመኸር እርሻ 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን መታቀዱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር የ2018/19 የመኸርና የበልግ ወቅት የሰብል ልማት ንቅናቄን በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በመግለጫቸው እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የመኸር፣ የበልግና የበጋ መስኖ ልማት ስራዎች በተቀናጀ መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ።

"ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነት በሀገር ደረጃ ማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ የሰብል ምርትን በመሬት ሽፋንና በምርታማነት ማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለግብርና ስራ ምቹ የሆነ የሰብል ልማት ስነ-ምህዳር ያላት በመሆኑ፣ በክልሎች የሚገኙ ጸጋዎችን በመለየት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።

ከ2011/12 የምርት ዘመን ጀምሮ በመኸር፣ በበልግ እንዲሁም በስንዴ ልማትና በሌሎች ምርቶች የሚታረስ መሬት በመጠንም ሆነ ከሄክታር የሚገኘው ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡

ለአብነትም በ2011 ዓ.ም በ3 ሺህ 500 ሄክታር መሬት ላይ የተጀመረው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ዘንድሮ 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መድረሱን ገልጸዋል፡፡

በዚህም መጀመሪያ ላይ ይገኝ የነበረው 100 ሺህ ኩንታል ምርት፣ በዘንድሮው ዓመት ወደ 175 ሚሊዮን ኩንታል ከፍ ማለቱን ተናግረዋል፡፡

የመኸር ስንዴ ልማት በ2011 ዓ.ም ከነበረው 1 ነጥብ 75 ሚሊዮን ሄክታር ሽፋን በአሁኑ ወቅት ወደ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ማደጉን ጠቅሰዋል፡፡

በመኸር የሰብል ልማት የእርሻ መሬትና በሄክታር የሚገኝ ምርታማነት በየዓመቱ እያሳየ የመጣውን ጭማሪ ተከትሎ ለቀጣዩ የ2018/19 የመኸር ወቅት 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ግብ መቀመጡን ተናግረዋል፡፡

ለበልግ እርሻ 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እስካሁን 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ለተመዘገበው ስኬት የአመራሩ ቁርጠኝነት ወሳኝ ሚና መጫወቱንም አንስተዋል፡፡

የኩታ ገጠም እርሻ መስፋፋት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን ማሽነሪዎች አቅርቦት ማደግ፣ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር አቅርቦት መሻሻል ለግብርናው ዘርፍ እድገት ተጠቃሽ ምክንያቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025