የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮ ቴሌኮም ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመተባበር አገልግሎቶችን ይበልጥ የሚያዘምን ቴሌሳይን (teleSign) የተሰኘ ዲጂታል ሶሉሽን አስጀመረ

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ከፍትህ ሚኒስቴር እና ከፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር በመተባበር የመንግስት አገልግሎቶችን ለማዘመን ያለመ ቴሌሳይን (teleSign) የተሰኘ የዲጂታል ሶሉሽን አስጀምሯል።


በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬሕወት ታምሩ፤ኩባንያው የሀገሪቱን የዲጂታል ሽግግር እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ግዙፍ የቴክኖሎጂ መሰረተ-ልማቶችን በስፋት እየዘረጋ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


አዲሱ ቴሌሳይን የተሰኘው ዲጂታል ሶሉሽን በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን አስረድተዋል።


ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ውጤት አስተማማኝ የዲጂታል ማንነት ማረጋገጫንና ህጋዊ ተቀባይነት ያለውን የዲጂታል ፊርማ ስርዓት ወደ ስራ የሚያስገባ ነው ብለዋል።


ይህም የመንግሥት አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታል በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል ነው ያሉት።


አሠራሩ በተለይም አሰልቺ ቢሮክራሲን በመቀነስ፣የአገልግሎት ተደራሽነትን በማሳደግ እና ሀገራዊ የዲጂታል ተጠቃሚነትን በማስፈን ረገድ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖረው ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።


የዲጂታል አገልግሎት መስጫው ዜጎች ያለ ምንም መልክዓ-ምድራዊ ገደብ የመንግስት አገልግሎቶችን በኦንላይን እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ጠቅሰዋል።


ይህም ሀገሪቱ ወደ ሙሉ ዲጂታል መንግሥት (E-Government) የምታደርገውን ሽግግር በእጅጉ የሚያፋጥን ሲሆን፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ዜጎች አገልግሎቶችን በፍጥነት፣ በብቃትና በታማኝነት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ብለዋል።


ኢትዮ ቴሌኮም መሰል ዘመናዊ የዲጂታል መፍትሔዎችን በማቅረብ፣ሀገራዊ የዲጂታል ጉዞን የመደገፍና የማብቃት ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አፅንኦት ሰጥተዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ፤ ሚኒስቴሩ የተጣለበትን ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን ተቋማዊ ለውጥ እያካሄደ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


አገልግሎት አሰጣጡን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማሻሻል ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ሲሆን፥የዲጂታል አገልግሎት መጀመሩም ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ነው ብለዋል።


ሚኒስቴሩ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመቀናጀት የቴሌሳይን (teleSign) እና ዲጂታል ሞፋ (Digital MoFA) የተሰኙ ቴክኖሎጂ መር አገልግሎቶችን በይፋ መጀመሩን ተናግረዋል።


የዲጂታል ሥርዓቶቹ ከየትኛውም ቦታ ሆነው እንዲህ አይነት ዘመናዊ አገልግሎት ለማግኘት ሲናፍቁ ለነበሩ የዲያስፖራ አካላትና መላው ዜጎች ትልቅ የምስራች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


በተጨማሪ ህጋዊ ተቀባይነት ያለውና የሰነዶችን ኦሪጅናልነት የሚያረጋግጥ የዲጂታል ፊርማ ስርዓትን ስራ ላይ ማዋል ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።


የላቁ የኢንክሪፕሽን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ሰነዶች እንዳይለወጡና እንዳይጭበረበሩ ብሄራዊ ዋስትና መስጠት እንዲሁ።


አገልግሎቱን ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር በማስተሳሰር፣ የተገልጋይ ማንነት ማረጋገጫ ስርዓት መዘርጋቱንም ጠቅሰዋል።


ዲጂታል አገልግሎቱ በውጭ ጉዳይ፣በሰነዶች ማረጋገጫ እና በፍትህ ሚኒስቴር መካከል የተቀናጀ የመረጃ ፍሰት እንደሚፈጥርም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025