🔇Unmute
አምቦ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በ220 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች በሚቀጥለው ክረምት የሚተከል የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ የቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ አቶ ቶሎሳ አራርሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ አርሶ አደሩን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በቡናና ፍራፍሬ ልማት በማሳተፍ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እየተሠራ ይገኛል።
ለዚህም በመጪው ክረምት 5 ነጥብ 7 ሚሊዮን የቡና ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ፣ እስካሁን 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል።
እንደ ቡድን መሪው ገለጻ፤ ችግኞቹ ከጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች ሲሆኑ፣ በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውና በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት መስጠት የሚጀምሩ ናቸው።
የችግኝ ዝግጅቱ በ220 የመንግሥትና የግል የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እየተከናወነ ሲሆን፣ በሥራው ላይ 16 ሺህ 415 አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
የተዘጋጀው የቡና ችግኝ ሲተከል አንድ ሺህ ሄክታር ገደማ አዲስ መሬት በቡና መሸፈን እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል።
ከአዲስ ተከላው በተጓዳኝ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ዛፎችን የማደስ ሥራም እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025