የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአፋር ሕዝብ በረሃውን በማለምለምና የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ጥንካሬ በመገንባት አለኝታነቱን ዳግም እያደሰ ይገኛል

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፋር ሕዝብ በረሃውን በማለምለምና የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ጥንካሬ በመገንባት አለኝታነቱን ዳግም እያደሰ ይገኛል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተንዳሆ መስኖ ልማት የማጠናቀቂያ እና መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ መርቀዋል።


የአፋር ሕዝብ በረሃውን በማለምለምና የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ጥንካሬ በመገንባት አለኝታነቱን ዳግም እያደሰ ይገኛል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ለእኛ ሉዓላዊነት ማለት ዳር ድንበርን ከመጠበቅ ባሻገር፣ የዜጎችን አንገት የሚያስደፋውን የልመና እጅ ሰብሮ በራስ ምርት መቆም ነው ብለዋል።

የአፋር ሕዝብ ለዘመናት የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በንቃትና በጀግንነት ሲጠብቅ የኖረ የቁርጥ ቀን የሀገር ባለውለታ መሆኑንም አውስተዋል።

ለምርቃት የበቃው የተንዳሆ መስኖ ልማት የማጠናቀቂያ እና መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት፣ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ትግላችን የድል ዓርማ ነው ብለዋል።

ለዓመታት ተጓትቶ፣ ተስፋ አስቆርጦና የጎርፍ ሥጋት ሆኖ የቆየውን ግድብ፣ በቆራጥ አመራርና በፈጣን አፈጻጸም ወደ ልማት አውታር መቀየሩን ተናግረዋል።

ይህ ፕሮጀክት ለምድራችን በረከት፣ ለሕዝባችን የብልጽግና ምንጭ እንዲሆን ዳግም ተወልዷል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

እውነተኛ ነጻነትና ምሉዕ ክብር የሚረጋገጠው በራስ ማሳ ላይ በሚለማ ሰብል፣ በራስ ጉልበት በሚገራ ውኃና ከማንም እጅ በማይጠበቅ የዜጎች የዕለት ጉርስ መሆኑንም አመልክተዋል።


የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተነሣነውም የዜጋን ክብርና የሀገርን የህልውና መሠረት ለማጽናት ነው የዚህ ዋናዎቹ ዐቅሞቻችን ደግሞ ያልተነካው የበረሃ ለም አፈራችን፣ ውኃችን፣ ትጉህ ሕዝባችንና የመስኖ አውታሮቻችን ናቸው ብለዋል።

ለእኛ መስኖ ማለት የዝናብ ጠባቂነትን ታሪክ መዝጋት ነው፤ መስኖ ተለዋዋጭ የሆነውን የዓለም ጂኦ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ውጥረት የምንቋቋምበት ብቸኛውና አስተማማኙ መከታችን ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የቆላማ አካባቢዎቻችንን እምቅ ሀብት ማልማትና የዜጎቻችንን ሕይወት በዘመናዊ የኮሪደር ልማት ማሣለጥ የወደፊት ዕጣ ፈንታችንን የመወሰን ጉዳይ እንደሆነም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።

ቃልን በተግባር፣ ሐሳብን በውጤት እየለወጥን፣ አርሶ አደሩን፣ አርብቶ አደሩንና ባለ ሀብቱን ያስተሣሠረ የልማት ሠንሰለት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያን በምግብ ራሷን የቻለች ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም የምትተርፍ የብልጽግና ተምሳሌት እናደርጋታለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025