የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰቡን የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ነው

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅግጅጋ ፤መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰቡን የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን በጥናት እና ምርምር እያገዘ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ሙሳ መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሶማሌ ክልል ውኃ ቢሮ አዘጋጅነት ዓለም አቀፍ የውኃ ቀንን ምክንያት በማድረግ የምክክር መድረክ በዩኒቨርሲቲው ተካሂዷል።


የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ሙሳ መሐመድ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ውኃ ለማንኛውም ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ወሳኝ ነው።

በመሆኑም በዚህ ዘርፍ የሚከናወኑ ሥራዎች በተለይ እንደ ሶማሌ ክልል ላሉ ቆላማ አካባቢዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲውም ይህንን ታሳቢ በማድረግ ከክልሉ ውኃ ቢሮና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ እያከናወናቸው ካሉ ተግባራት መካከል ተማሪዎችን በገጸ-ምድርና በከርስ-ምድር ውኃ ልማት ዘርፎች ማሰልጠንና ማስመረቅ አንዱ መሆኑን አንስተዋል።

በተጨማሪም በውኃ ሀብት ልማት ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥናት እና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የውኃ እጥረት ያለባቸውን አካባቢዎችን በተለያዩ መንገዶች የመደገፍ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።


የሶማሌ ክልል ውኃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ መሐመድ በበኩላቸው፤ መንግሥት የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተደራሽነትን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የክልሉ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ሽፋን 51 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፣ በገጠርና በከተሞች ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

በመድረኩ ላይ ምሁራን እና ባለድርሻ አካላት የውኃ አገልግሎት ተቋማትን የማስተዳደር አቅም ማጎልበት እንዲሁም ቴክኖሎጂን በመጠቀም የውኃ ተጠቃሚነትን ማስፋፋት ትኩረት ሊያገኙ ይገባል ብለዋል።

የውኃ ፕሮጀክቶች በቋሚነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል የጥገናና የክትትል አቅምን ማሳደግ እና ኅብረተሰቡ በዝናብ ወቅት ውኃን የመቆጠብና የመጠቀም ግንዛቤው እንዲጎለብት መስራት ከባለድርሻ አከላት የሚጠበቅ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025