🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦መንግስት የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስታት የመሰረተ ልማት ግንባታን ለገበያ ከመስጠት ይልቅ በዘርፉ መዋዕለ ንዋይ የማፍሰሳቸው ተገቢነትን በተመለከተ በሰጡት ማብራርያ፤ በዓለም ላይ መንግስት ሳይገባበት የተገነባ መሰረተ ልማት አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡
ሀገራት መሰረተ ልማቶች ከተገነቡና የማህበረሰብ እውቀትና ሀብት ከሆኑ በኃላ ገንዘብ እንዲያመጡ ወደ ግል ማሸጋገር እንደሚፈልጉም አንስተዋል፡፡
ለዚህም ከዛሬ 50 ዓመት በፊት የግል ሳተላይት የሚያመጥቅ እንዳልነበረ እና አሁን ላይ ከሀገራት ባለፈ ግለሰቦችና ኩባንያዎች ጭምር እንደሚያመጥቁ ለአብነት አውስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከፍተኛ መዋዕለንዋይ የሚፈልጉ በመሆኑ ለባለሀብት መስጠት አዳጋች መሆኑንና ነገር ግን ወደፊት ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
በዘርፉ መንግስት መሳተፉ ለኢኮኖሚው ሞተር በመሆኑ የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ ወደፊትም በሰፊው መሳተፉ የሚቀር እንዳልሆነም ጠቁመዋል፡
ይህም የገቢ አቅምን ለመጨመር፤ኢኮኖሚያዊ ፍትሃዊነትን እንዲሁም የኑሮ ጥራትን ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል፡፡
ወደፊትም ማህበረሰቡን በብዙ መልኩ የሚጠቅም በመሆኑ መንግስት የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025