የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

መንግስት በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት ይጥላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት እንደሚጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በቆይታቸውም የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ፤ እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸው ፋይዳ በጥልቀት ተዳሷል።

ኢትዮጵያ ውብ፣ ታላቅና በስልጣኔ ቀደምት የሆነች ሀገር ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ የራሷ አቆጣጠር ያላት፣ በአፍሪካ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ ሀገር፣ የሰው ልጅ መገኛ ቡናን ለዓለም የሰጠች ሀገር መሆኗንም አውስተዋል።

ይህም ኢትዮጵያ ተቀባይ ብቻ ሳትሆን ለዓለም አስተዋጽኦ ማድረግ የሚያስችል ብቃት ያለው ህዝብ እንዳላት የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያን ከአጭር ጊዜ ይልቅ አርቆ በማየትና በማሰብ በትብብር ከገነባን ለብዙዎች ብርቅ ለብዙዎች መጠለያ ለብዙዎች መሸሸጊያ የምትሆን ሀገር መፍጠር ይቻላል ነው ያሉት።

ከ1 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ፍልሰተኞችን ተቀብላ ማስተናገዷን ጠቅሰው ሀገርን በወግ እና በስርዓት መገንባት ከተቻለ ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ አድርጎ መስራት እንደሚቻል አመልክተዋል።

የሰው ልጅ የተሰጠው ጊዜ ውስን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠን ጊዜ በተገቢው ሁኔታ መስራትና ለልጆች የሚታወስና የሚጠቅም ነገር ማድረግ አለብን ብለዋል።

በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት ጥለን እናልፋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካውም በኢኮኖሚውም በዲፕሎማሲውም በወታደራዊ አቅሙም ለትውልድ አስቻይ የሆነ መሰረት ጥለን እንደምናልፍ ተስፋ አለኝ ብለዋል።

ይሄ ነገር እንዳይሳካ የሚያደናቅፉ ኃይሎች ሊኖሩ ቢችሉም እኛ እንቅፋቶቻችንን ከመንገዶቻችን እያስወገድን ያሰብነውን ለማሳካት በተሰጠን ጊዜ ቀንና ለሊት እንተጋለን ልጆቻችን ያስቀጥሉታል ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ ድንቅ መሆኗን ታሪክ ጠገብ መሆኗን ሀብታም መሆኗን በንግግር ሳይሆን በተግባር ገልጠን የምናሳይበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት እና የግዙፍ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በስኬትና በለውጥ ላይ የምትገኝበት ወቅት መሆኑንም ገልጸዋል።

የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተግተን ከሰራን የወደፊቷ ያማረ እና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር እንደሚቻል ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025