🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት የመልካም አስተዳደር ውጤታማነትን እያረጋገጠ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 3ኛውን የ'አዲስ መሶብ' ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የልደታ ቅርንጫፍን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

በዚሁ ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደተናገሩት፤ የመንግስትን አገልግሎቶች ጥራትና ውጤታማነት የሚያስጠብቅ አስቻይ ምኅዳር እየተፈጠረ ነው።
በዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነት የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የተገልጋዮችን እርካታ እያሻሻለ ይገኛል ብለዋል።
በመሶብ የአንድ ማዕከል የሚሰጡ አገልግሎቶች ጥራትና ውጤታማነትን በማስጠበቅ ብልሹ አሰራሮችን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ማስቻሉን ተናግረዋል።

በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የተገኘው ተጨባጭ ውጤት ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ለዜጎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መፍትሔ መስጠቱን ገልጸዋል።
በመዲናዋ የተገነቡ የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከላት የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎት በማፋጠን የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በቀጣይም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ የተገልጋዮችን እርካታ የማሻሻል ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025