የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የኃይል ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት በትኩረት እየሰራች ነው-ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የኃይል ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት በትኩረት እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ኃብት በመጠቀም በካይ ያልሆኑ የኃይል ምንጮችን ለማልማት የረጅም ጊዜ ስትራቴጂ ነድፋ እየሰራች የምትገኝ ሲሆን የውሃ ኃይል፣ የንፋስና ፀሐይ ኃይል እንዲሁም የጂኦተርማል ተጠቃሾች ናቸው፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት ከምትጠቀመው አጠቃላይ የኃይል ምንጭ ውስጥ ከ96 በመቶ በላይ የሚሆነው በካይ ካልሆኑና ታዳሽ ከሆኑ ምንጮች የሚገኝ ነው።

ይህም ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ኢነርጂ ልማት ረገድ ቀዳሚ ተጠቃሽ ሀገር እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።

የውሃ ኃይል (Hydro) ትልቁን የኃይል ድርሻ የሚይዝ መሆኑን ጠቅሰው፥ የፀሐይና የንፋስ ኃይል ቴክኖሎጂዎችም በስፋት ወደ ስራ እየገቡ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ይህ ስኬት መንግስት ሀብቱን ወደዚህ ዘርፍ ለማዞር ባሳለፈው ፖሊሲ ተኮር ውሳኔ የተገኘ መሆኑን ጠቁመው፥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የዚህ ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ትልቁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

መንግስት የዜጎችን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በአረንጓዴ ኢነርጂ ልማት ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ከሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኘው አጠቃላይ የኃይል መጠን ከ10 ጊጋ ዋት በላይ መድረሱ ከፍተኛ ሀገራዊ አቅም መፈጠሩን ያሳያል ብለዋል።

የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስና የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ ከነዳጅ ነፃ የሆኑ አማራጮችን ማስፋፋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አሳስበው በየደረጃው የታቀዱ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025