የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ዛምቢያ እና ሞዛምቢክ ከኢትዮጵያ የስንዴ ምርትና የሌማት ትሩፋት ስኬት ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉ ገለጹ

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ኢኒሼቲቭና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ካስመዘገበችው ስኬት ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በአዲስ አበባ እየተካሄደ ካለው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በተጓዳኝ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል።


ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ እና ከሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢ እና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ ጋር ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ ማሻሻያዎችን በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማግኘቷን አብራርተዋል፡፡

እንዲሁም በንግድና ሌሎች ዘርፎች ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እያከናወነች ያለውን ተግባር አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ ቡናን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለውጭ ገበያ እያቀረበች መሆኗን በመግለጽ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመጠቀም አህጉራዊ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል።

ከሁለቱ ሀገራት ጋር በተለያዩ የግብርና ዘርፎች በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ትብብሮችን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

የዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ በበኩላቸው ሀገራቸው በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በስንዴ፣ በሌማት ትሩፋት እና በሌሎች የግብርና ዘርፎች ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉም ጠቁመዋል።

ዛምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት በመፈራረም በዘርፉ በጋራ መስራት እንደምትፈልግ ሚኒስትሩ አንስተዋል።

የሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጠንካራ የግብርና ሥርዓት በመገንባት ካስመዘገበችው ስኬት ትምህርት መውሰድ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

በተለይም የስንዴ ምርትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት የተመዘገቡ ስኬቶች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ነው ያነሱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025