የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዓለም አቀፍ ደረጃ የምግብ ምርትን ለማሳደግ ሀገራት ትብብራቸውን የበለጠ ሊያጠናክሩ ይገባል-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦በዓለም አቀፍ ደረጃ የምግብ ምርትን ለማሳደግ እና የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ሀገራት ትብብራቸውን የበለጠ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ።

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ካለው የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በተጓዳኝ እ.ኤ.አ የ2025 የዓለም የምግብ ዋስትናና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ሁኔታን የተመለከተ ሪፖርት ትናንት ምሽት ይፋ ሆኗል።


ሪፖርቱ የአየር ንብረት ለውጥና የተለያዩ ግጭቶች የዓለም የምግብ አቅርቦትና ዋጋ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን አመላክቷል።

ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በሪፖርቱ ይፋ ማድረጊያ መርሃግብር ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በዓለም ላይ እየጨመረ የመጣው የምግብ እጥረትና የዋጋ መናር የሀገራት የጋራ መፍትሔ ያስፈልገዋል ብለዋል።

ችግሩ በተለይም አነስተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን የበለጠ የሚጎዳ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደች መሆኑን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የምግብ ዋጋ መናርን ለመቀነስ እየተወሰዱ ባሉ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውንም ነው የጠቀሱት።

በልማት ሴፍትኔት መርሃ ግብርም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዓለም ላይ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦትን ለማረጋገጥ፣ ምርታማነትን ለመጨመር እና ሰላምን ለማፅናት ሀገራት በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባ ነው ያመለከቱት።


የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሀመድ በበኩላቸው፤ የምግብ ዋጋ እየጨመረ መምጣት በርካታ የዓለም ዜጎች የምግብ ዋስትናቸው እንዳይረጋገጥ ማድረጉን ነው ያነሱት።

የአየር ንብረት ለውጥና የተለያዩ ግጭቶች የዓለም የምግብ አቅርቦትና ዋጋ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸውንም አንስተዋል።

በዓለም በርካታ ህፃናት በምግብ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው መቅረታቸውንም ነው ያነሱት።

በዓለም ላይ ግጭትን ማስቀረት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለዚህ ደግሞ የጋራ ትብብርና ተግባራዊ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር) በበበይነ መረብ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ የተፈጥሮ አደጋዎችና ግጭት ለጤና አስፈላጊ ምግቦች አቅርቦት ላይ እጥረት ፈጥሯል።

ይህ የምግብ ሥርዓት መዛባት በርካታ ዜጎችን ለጤና እክል ተጋላጭ ማድረጉንም አንስተዋል።

የዓለም መንግስታት የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች በምግብ ሥርዓት ላይ እያደረሰ ያለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለመከላከል የበለጠ ትብብራቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025