አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን በመጠቀም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ።
ከሁለተኛ የምግብ ስርዓት ጉባኤ ጎን ለጎን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል።
ሚኒስትሮቹ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በውይይታቸው አንስተዋል።
የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያላትን አቅምና እያከናወነች ያለውን ተግባር አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ቡናና የእንስሳት ውጤቶችን ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እንደምትልክ ገልጸው፤ ይህንን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
ኢትዮጵያ በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በርካታ አማራጮች እንዳላት በመጥቀስ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች በግብርና ማቀነባበሪያ፣ማዳበሪያ ፋብሪካና ሌሎች ዘርፎች መሰማራት የሚችሉባቸው አማራጮች እንደሆኑ አብራርተውላቸዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸውዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሚኒስትሮች በሁለቱ አገራት መካከል በግብርና፤ንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን ለመጠቀም ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ለመስራት ተስማምተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025