የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፤ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አረጋገጡ

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን በመጠቀም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ።

ከሁለተኛ የምግብ ስርዓት ጉባኤ ጎን ለጎን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል።

ሚኒስትሮቹ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በውይይታቸው አንስተዋል።

የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያላትን አቅምና እያከናወነች ያለውን ተግባር አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ ቡናና የእንስሳት ውጤቶችን ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እንደምትልክ ገልጸው፤ ይህንን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

ኢትዮጵያ በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በርካታ አማራጮች እንዳላት በመጥቀስ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች በግብርና ማቀነባበሪያ፣ማዳበሪያ ፋብሪካና ሌሎች ዘርፎች መሰማራት የሚችሉባቸው አማራጮች እንደሆኑ አብራርተውላቸዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸውዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ሚኒስትሮች በሁለቱ አገራት መካከል በግብርና፤ንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን ለመጠቀም ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ለመስራት ተስማምተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025