የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በብሔረሰብ አስተዳደሩ ለምርት ዘመኑ 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ ዋለ

Jul 23, 2025

IDOPRESS

ሰቆጣ ፤ ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ለ2017/2018 የምርት ዘመን 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ መዋሉን የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ ይህንኑ ግብአት ተጠቅመው የእርሻ ስራቸውን በወቅቱ ለማከናወን ይበልጥ እንደጠቀማቸው በአስተዳደሩ የሰቆጣ ወረዳ አርሶ አደሮች ገልጸዋል።

የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ ውሏል።


የአርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ልምድ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በዚህም የሰብል ምርታማነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ የተጠናከረ የባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ጥቅም ላይ ከማዋልም ባለፈ እርጥበትን ማቀብ የሚያስችሉ አነስተኛ ጉድጓዶች በማሳ ላይ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሳይዳ ቀበሌ አርሶ አደር ይመር አበበ በሰጡት አስተያየት፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ቀጣይነት ያለው ምርታማነትን ለማሳደግ አጋዥ እንደሆናቸው ተናግረዋል።


በየዓመቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እያዘጋጁ ተጠቃሚ እንደሆኑና ወጪም እንደቀነሰላቸው አውስተው፤ ለዘንድሮው የመኽር እርሻ በግብአትነት የሚውል ሶስት ሜትር ስፋት በሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ በባለሙያ ታግዘው በመቆፈር የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

በበጋ ወራት ያዘጋጁትን ማዳበሪያም በግማሽ ሄክታር የእርሻ መሬታቸው ላይ ጥቅም ላይ አውለው ስንዴ መዝራታቸውን አርሶ አደር ይመር ተናግረዋል።

ሌላው አርሶ አደር ገብረየስ በለጠ በበኩላቸው፤ 60 ኩንታል የተፈጥሮ ማዳበሪያ በፍግ አዘጋጅተው በእርሻ ማሳቸው ላይ በመበተን ጥቅም ላይ እንዳዋሉ ገልጸዋል።


የተፈጥሮ አፈር ማዳበሪያ መጠቀም መቻላችን ዘላቂ የሆነ የአፈር ለምነትን ጠብቆ ያቆይልናል ያሉት አርሶ አደር ገብረየስ፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ የእርሻ ስራቸውን በወቅቱ ለማከናወን ይበልጥ እንደጠቀማቸው አስረድተዋል።

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በምርት ዘመኑ 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በተለያየ የሰብል ዘር ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከግብርና መምሪያው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025