
ሆሳዕና፤ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄና የልማት ፍላጎት በአግባቡ በመገንዘብ ምላሽ መስጠት የሚችል አመራር የመፍጠር ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃዎች ላይ ለሚገኙ የክልሉ አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሆሳዕና ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።

በዚሁ መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር)፤በዚህ ዘመን ወቅቱን የዋጀና የህዝቡን ፋላጎት በአግባቡ በመረዳት ሌት ተቀን መስራት የሚችል አመራር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጣን መፍትሄ የሚሰጥ በእቅድ የሚመራ እና ህዝብን በቅንነት የሚያገለግል ብቁና ጠንካራ አመራር መፍጠር ይገባል ብለዋል።
የመድረኩም ዓላማ ይህንኑ መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ አመራሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ እውነተኛ የህዝብ አገልጋይ ለመሆን ራሱን እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።
በሀገሪቷ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሁሉም መስኮች አስደናቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አንስተው፥ የተቀመጠውን የብልጽግና መዳረሻ ለማሳካት ከመቼውም ጊዜ በላይ የአመራሩ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ብለዋል።
በየደረጃው ያለው አመራር የህዝብን አቅም በማስተባበር ክልሉን ብሎም ሀገርን የሚለውጡ የልማት ስራዎችን ለማሳካት መትጋት አለበት ሲሉ ተናግረዋል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025