
በሁለተኛው ምእራፍ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ምን። እየተከናወነ ነው?
• ሁለተኛው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ስራ በአዲስ አበባ በ8 አካባቢዎች እየተከናወነ ነው።

• በሁለተኛው ምእራፍ የሚከናወነው የኮሪደር ልማትበአጠቃላይ 2 ሺህ 879 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፤ 240 ኪሎ ሜትር የአስፋልት እንዲሁም 237 ኪሎሜትር እግረኛ መንገድ በመገንባት ላይ ነው።

• በስምንቱም የኮሪደር ልማት ስፍራዎች 32 የህጻናት መጫዎቻዎች ፤79 የሚሆኑ ህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም 114 የመኪና መቆሚያ ፓርኪንግና የታክሲና አውቶብስ ተርሚናሎችን ያከተተ መሰረተ ልማት ይከናወናል።

• ከትራንስፖርት መሰረተ ልማቶች መካከል 58 በሚሆኑ አካባቢዎች ላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ጣቢያዎች ይኖራሉ።
• ከ100 ኪሎሜትር በላይ የሚሆን የብስክሌት መንገድም በመገንባት ላይ ነው።

• የከተማዋ ነዋሪዎች ጤናቸውን የሚጠብቁባቸው 17 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ተገንብተውለአገልግሎት ክፍት ይደረጋሉ።
• በኮሪደር ልማት ስራው ከእንጦጦ -ቀበና-ግንፍሌ ፒኮክእንዲሁም ከእንጦጦ-ወዳጅነት-ፒኮክ የሚደርሱ ሁለትየወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችም እየተከናወኑ ነው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026