
ጭሮ/ጊምቢ/መቱ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሶስት ዞኖች ባለፉት ስድስት ወራት ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች እንዲሰማሩ መደረጉን የየዞኖቹ ስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ጽህፈት ቤቶች ገልጸዋል፡፡
የስራ እድሉ የተፈጠረው በክልሉ ምዕራብ ሐረርጌ፣ ምዕራብ ወለጋ እና ኢሉአባቦር ዞኖች ሲሆን ወጣቶቹም በስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የክህሎት ስልጠና የብድርና የማምረቻ ቦታ መሰጠቱም ተገልጿል።
የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራ እና ክህሎት ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ አይናለም ጌታቸው እንዳሉት ባለፉት ስድስት ወራት ከ46 ሺህ 900 በላይ ወጣቶች በማህበራት ተደራጅተው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡
ለወጣቶቹ ከ76 ሚሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ከ1 ሺህ ሄክታር በላይ የመስሪያ ቦታ ማቅረብ እንዲሁም የሙያ ስልጠና መሰጠቱን አብራርተዋል፡፡
የምዕራብ ወለጋ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራ እና ክህሎት ጽህፈት ቤት የከተማ ስራ ዕድል ፈጠራ ቡድን መሪ አቶ ሀምቢሳ ተርፋ፤ በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት ከ99 ሺህ በላይ ወጣቶችን በገጠርና በከተሞች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ለወጣቶቹ ከ2 ሺህ ሄክታር በላይ የመስሪያ ቦታ መሬትና ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ በኢሉአባቦር ዞን ባለፉት ስድት ወራት ከ58 ሺህ 800 በላይ ወጣቶች በተለያዩ የስራ መስኮች የስራ ዕድል መፈጠሩን የዞኑ የስራ ዕድል ፈጠራና ሙያ ጽህፈት ቤት የዕቅድ ግምገማና ክትትል ስራ ሂደት መሪ አቶ ወንድሙ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
የስራ እድል ከተፈጠረላችው ወጣቶች መካከል በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በጭሮ ከተማ በማህበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ የተሰማሩት ወጣት ሚሊኪ ያኪ እና ጓደኞቹ በተመቻቸላቸው የ500 ሺህ ብር ብድር በጀመሩት ስራ ውጤታማ በመሆኑ ብድሩን ከመመለስ አልፎ ከ200 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግሯል፡፡
የዚሁ ከተማ ወጣት ደምሴ ከተማ ከአምስት ጓደኞቹ ጋር በመደራጀት 100 ሺህ ብር ተበድረው በጀመሩት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ጥገና እና ንግድ ስራ ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በምዕራብ ወለጋ ዞን፤ ወጣት ዳንኤል ዱጋሳ ከጓደኞቹ ጋር በማህበር የጀመሩት የሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ ውጤታማ እያደረጋቸው መምጣቱን አስረድተዋል፡፡
ከስራ እድል ተጠቃሚዎች መካከል በኢሉአባቦር ዞን ሀሉ ወረዳ በሻይ ልማት መስክ የተሰማራው ወጣት ታረቀኝ አስፋው እንዳለው የሻይ ቅጠልን ለገበያ በማቅረብ ገቢውን ለማሳደግ እየሰራ ነው፡፡
የዞኑ መንግስት ብዝሀ ኢኮኖሚን ለማስፋት ለሻይ ልማት የተሰጠው ትኩረትና ምርቱ በገበያ ተፈላጊ መሆኑ ገቢውን እንዳሳደገለት ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026