የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ፕሮጀክቱ የከተማዋን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ እያደረገ ነው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)የ፦ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ከተማ አስተዳደሩ ገለፀ።

ስማርት አዳማ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በአገልግሎትና የአሰራር ማሻሻያ ጭምር በጥናት ላይ የተደገፉ ተግባራት ፕሮጀክት ያቀፈ ነው።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ በሪሶ ዶሪ ለኢዜአ እንዳሉት በከተማዋ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል የስማርት አዳማ ፕሮጀክት እየተተገበሩ ነው።

ለፕሮጀክቱ ትግበራ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኢትዮ ቴሌኮምና አርተፊሻል እንቴለጀንስ ከፍተኛ ድጋፍና እገዛ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፕሮጄክቱ የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በፕሮጀክቱ በከተማዋ የሁሉም መስሪያ ቤቶች ሰነዶችን ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ መሆኑን ገልጸው፤ የመሰረተ ልማት፣ የትፊክ ፍሰት፣ የትራንስፖርት አገልግሎትና የጸጥታ ተቋማትን ለአብነት አንስተዋል።

ከ81 ሺህ በላይ የመሬት አሰተዳደርና አጠቃቀም ፋይሎች ወደ ዲጂታል በመቀየር ሌብነትና ብልሹ አሰራርን ጨምሮ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።

የኢትዮ-ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ለስማርት አዳማ ፕሮጀክት አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማትና የኮደርስ ስልጠናም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026