
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ)፦የጥምቀትበዓልከኃይማኖታዊእሴቱባሻገርየከተማዋንመልካምገጽታበማስተዋወቅየኢኮኖሚተጠቃሚነታቸውንእያረጋገጠላቸውመሆኑንየባቱከተማነዋሪዎችገለጹ፡፡

በባቱ ከተማ ደምበል ኃይቅ ላይ የሚከበረውን የጥምቀት በዓል ለመታደም ወደ አካባቢው የሚመጡ እንግዶች መልካም ቆይታ እንዲኖራቸው አስፈላጊውን ሁሉ ማዘጋጀታቸውን በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ገልጸዋል፡፡
የጥምቀት በዓል ከኃይማኖታዊ እሴቶች ባሻገር በርካታ ማህበራዊና ባህላዊ ትውፊቶች የሚንጸባረቁበት ነው።

በባቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓልም በርካታ ቱሪስቶች የሚሳተፉበት መሆኑን ተከትሎ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል።
ባቱና አካባቢው የቱሪስት ኮሪደር መሆኑን ተከትሎ የአካባቢውን የተፈጥሮ፣ የባህልና የቱሪስት መስህብ የበለጠ በማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥርም ነው፡፡

በባቱ ከተማ ደምበል ኃይቅ ላይ በማህበር ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉ ወጣቶች በጥምቀት በዓል አከባቢያቸውን በማስተዋወቅ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በኃይቁ በሞተር ጀልባ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጠው ወጣት ሳቃሳ በሪሶ በጥምቀት በዓል ለቱሪስቶች የጀልባ አገልግሎት በመስጠት አከባቢያቸውን እያስተዋወቁ ገቢም ለማግኘት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡

ለእንግዶች የተሟላ የጀልባ አገልግሎት በመስጠት ላይ እነደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡
በኃይቁ አካባቢ የዓሳ ምርቶችን በማቅረብ የሚተዳደሩት ወጣት ዙሪያሽ ግርማና አማኑኤል ወልደጊዮርጊስ፤ የጥምቀት በዓልን ለመታደም ወደ ከተማዋ የሚመጡ እንግዶች መልካም ቆይታ እንዲኖራቸው እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በኃይቁ ዳርቻዎች የዓሳ ምርቶችን ለቱሪዝቶች ለማቅረብ መዘጋጀታቸውንም ነው የጠቆሙት፡፡
ከምስራቅ ሀረርጌ በዓሉ ላይ ለመታደም የመጡት አቶ ሸዋንግዛው ንጉሴ በአካባቢው በተደረገላቸው መልካም አቀባበል መደሰታቸውን ተናግረዋል።
በኃይቁ ዳርቻ አካባቢዎች ያለውን ውብ መልካዐ ምድር ለማልማት የተደረገው ጥረትም እጅግ የሚያስደስት ነው ብለዋል፡፡
በአካባቢው የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ይበልጥ በማስፋፋት በርካታ ጎብኚዎችን ወደ ለመሳብ መሰራት እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡
ወይዘሮ ጫልቱ ቃበቶ በበኩላቸው ኃይቁን ለቱሪዝም ገቢ ለማዋል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026