የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በአክሱም ከተማ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አክሱም፣ጥር 6/2017 (ኢዜአ)፦በአክሱም ከተማ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማው ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ።

በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሐዱሽ ገብረመድህን ለኢዜአ እንደገለጹት፤በበጀት ዓመቱ የአክሱም ተለዋጭ መናኸሪያን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች እየተካሄዱ ነው።

የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ ለከተማዋ ነዋሪዎች የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው ብለዋል።

ከሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል የ1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣የመንገድ ዳር መብራትና የ5 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።

በተጨማሪም በክረምት ወራት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች 1 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የጎርፍ መውረጃ ቦይ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አብራርተዋል።

የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹም ለ1 ሺህ 400 ስራ አጥ ወገኖች የስራ እድል ተፈጥሯል።

የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል የንግስተ ሳባ ቀበሌ ነዋሪው ወጣት አቤሰሎም ዜናዊ ከሥራው በሚያገኘው ገቢ የመነሻ ካፒታል ተጠቅሞ የግሉን ስራ ለመጀመር ሀሳብ እንዳለው ገልጿል።

የሐወልቲ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሙሉ ካህሳይ በበኩሏ በተፈጠረላት የስራ ዕድል በምታገኘው ገቢ ወደ ዘላቂ ሥራ ለመሸጋገር እቅድ እንዳላት ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026