
በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ የሚታይ ምንነቱ ያልታወቀ ተቀጣጣይ ነገር መመልከታቸውን በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች በተለያዩ አማራጮች መረጃውን አጋርተዋል።
ተቀጣጣይ ነገሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፎቶ እና በተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ለመመልከት ተችሏል።
ጉዳዩ የብዙዎችንም ቀልብ የሳበ ጉዳይ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ስፔን ሳይንስ ሶሳይቲ ትናንት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸውን አስመልክቶ ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል።
ሶሳይቲው በደረሰው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ ባደረገው ምልክታ የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ ሲል አመልክቷል።
ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ነው ያስታወቀው።
የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት እንዲቻል ሁኔታውን በቅርበት እያጣራ እንደሚገኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እንደሚያቀርብ ገልጿል።
ይህ የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ ሶሳይቲው አሳስቧል።
በተጨማሪም ሶሳይቲው የቁስ አካላቱን አስመልክቶ እያደረገ ላለው ማጣራት የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ የቀረጿቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎች በመላክ ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026