የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስር ጽኑ መሰረት መጣሉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን በጉለሌ ክፍለ ከተማ 6ተኛውን አዲስ መሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል በይፋ መርቀዋል።

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት መጋቢት 24 ቀን ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሻገር ቃል ኪዳን የተገባበት ታሪካዊ ቀን ነው።

ሀገራዊ ለውጡ የመጣው ለሁሉም፣ ከሁሉምና በሁሉም ዜጋ ተሳትፎ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ ከለውጡ ወዲህ የሚታዩና ተጨባጭ የሆኑ በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡት በጋራ ጥረታችን ነው ብለዋል።

ይህ ለውጥ የፖለቲካ፣ የማህበራዊና የኢኮኖሚ ስብራቶቻችን እንዲጠገኑና ወደ ከፍታ እንድንጓዝ እጅግ ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

ባለፉት ዓመታት “እንሰራለን፤ እንችላለን!” በሚል መርህ በጋራ በተነሳንባቸው ጊዜያት፣ ከኋላ ቀር የፖለቲካ ባህሎች ተላቀን ችግሮችን በውይይትና በምክክር የመፍታት ሂደት ላይ መገባቱን ከንቲባዋ አመልክተዋል።

ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር ወደ ዘመናዊ እና ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚ ለመገንባት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውንም ነው ያነሱት።

በማህበራዊ ዘርፍም የተሰበሩ እሴቶችን በማከም ማህበራዊ ፍትህ እንዲነግስ የሚስችሉ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል።

በተለይም በከተማዋ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖችን፣ የሀገር ባለውለታዎችን፣ አቅመ ደካሞችን፣ አካል ጉዳተኞችንና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ከአስቸጋሪ ኑሮ አውጥተን የሰውን ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲኖሩ አድርገናል ብለዋል።

በትምህርት ዘርፍም ባዶ ምሳ ዕቃ ይዘው ወደ ትምህርት ገበታ ይመጡ የነበሩ ሕፃናትን እኩል በልተውና ለብሰው እንዲማሩ ከማድረግ ባለፈ፣ አዲስ አበባን ሕፃናትን ለማሳደግ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ መቻሉን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።

ሌላው ትልቅ ስኬት የመንግስት የተቋማት ስብራትን በመጠገን ነፃ፣ ገለልተኛና የአገልጋይነት መንፈስን የተላበሱ ጠንካራ ተቋማትን የመገንባት ሽግግር መሆኑን ገልጸዋል።

ለዘመናት የአገልግሎት ዘርፉን ለመለወጥ ሳይቻል ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትቦ የኖረ ቢሆንም፣ የለውጡ መንግስት ቃል በገባው መሰረት ችግሩን ሥር ነቀል በሆነ መልኩ የሚለውጥ 'መሶብ' ዲጂታል አንድ ማዕከልን በመተግበር ለተገልጋዩ እፎይታን ይዞ መምጣቱን አመልክተዋል።

የእነዚህ የለውጥ ፍሬዎች ዋንኛ ተጠቃሚ የሆነው የአዲስ አበባ ነዋሪም ማልዶ ወደ አደባባዮች በመውጣት የዘወትር ድጋፉን እንደገና ማጽናቱን ከንቲባዋ ተናግረዋል።

ጅማሬያችን ትላንት ቢሆንም ከህዝባችን ጋር ያሳካነው ድል እና የደረስንበት ርቀት ቀላል አይደለም ሲሉም አክለዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ሊያስቆም የሚችል ምንም ዓይነት ምድራዊ ኃይል እንደሌለ በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025