የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ እንደሚውል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የዲጂታል ግብይት ስርዓቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየተከናወነ ያለው የሳይበር ደሕንነት ስራ ውጤታማ መሆኑም ተገልጿል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት በቀጣይ አመት ሁለተኛው ዙር የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መርሐ ግብር ይጀመራል።

መርሐ ግብሩ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል በወረቀት ገንዘብ የሚካሔድ ግብይትን ማስቀረትና በወረቀት የሚካሔዱ አገልግሎቶችን የሚያስቀሩ እንደሆነም ነው የገለጹት።

በኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስርዓት በስፋት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ምቹ የግብይት ስርዓት ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ከዚህ ውስጥም በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የግብይት ስርዓቱን በማዘመን በወረቀት ገንዘብ የሚካሔድ ግብይትን ማስቀረትና ከወረቀት ንክኪ የፀዳ አገልግሎት ተግባራዊ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለፃ በመጀመሪያው ዙር የዲጂታል ኢትዮጵያ መርሐ ግብር የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በአሁኑ ወቅትም በ25 የመንግስት ተቋማት 800 በላይ አገልግሎቶች ዲጂታል ቴክኖሎጂን ተጠቅመው እየሰሩ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ባለፉት ጥቂት አመታት ቴሌብርና የንግድ ባንክ የዲጂታል አመራጮችን ጨምሮ በሌሎች የዲጂታል ዘርፎች በተካሔደው ግብይት በትሪሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ማዘዋወር ተችሏል ነው ያሉት።

በመሆኑም የግብይት ስርዓቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየተከናወነ ያለው የሳይበር ደህንነት ስራ ውጤታማ በመሆኑ እቅዱን ለማሳካት ምቹ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል።

እስካሁን ባለው ሒደት ከ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ መሆናቸውንም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025