የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ ኢንዱስትሪዎች ለበርካቶች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በተደረጉ የተቀናጁ ድጋፎች ወደ ማምረት የተመለሱ ኢንዱስትሪዎች ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸው ተገለጸ።

የድሬዳዋ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ሀርቢ ቡህ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው በተደረገው ድጋፍና ክትትል በግንባታ ላይ እና ተዘግተው የነበሩ በርካታ ኢንዱስትሪዎች ከ10 ሺህ ለሚልቁ ጎች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል።


ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶችን እና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን የማዳንና የማስገኘት ዐቅማቸው እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል በያዝነው የበጀት ዓመት ብቻ 11 ኢንዱስትሪዎች ተመርቀው ሥራ መጀመራቸውን ገልጸው፤ ፋብሪካዎቹ ከ1 ሺህ 500 በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል።

ከሁለት ወራት በኋላም ሥድስት ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።


የፌደራልና የአሥተዳደሩ ተቋማት የተካተቱበት ዘርፉን የሚደግፍ አሠራር ተዘርግቶ፤ የኢንዱስትሪዎቹን የዓመታት የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመንገድ፣ የውኃ፣ የኃይልና የአገልግሎት ጥያቄዎችን በፍጥነት የመፍታት ተግባር እየተከናወነ መሆኑም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025