የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክህሎትና ስነምግባር የታነፀ ትውልድ የማፍራቱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በክህሎት፣ በእውቀትና በስነምግባር የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።

የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት በቦሌ አራብሳ አካባቢ ያስገነባውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት ምረቃ እና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሀግብር አካሂዷል።


የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ በክህሎት የዳበሩ ህፃናትና ታዳጊዎችን ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ዛሬ የተመረቀው የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት በክህሎት በእውቀትና በስነምግባር የታነጸ ትውልድን ለማፍራት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል።

በክህሎትና በእውቀት የዳበረ ትውልድ የማፍራት ሀላፊነታችንን ሁላችንም ልንወጣ ይገባልም ብለዋል።


የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፤ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በርካታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በትምህርትና ስልጠና ዜጎችን ወደ ላቀ እውቀት ለማሸጋገር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።

የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት ችግር ፈቺ የሆኑ ዜጎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።


ትምህርት ቤቱ ታዳጊዎች በክህሎት የዳበረ እውቀት እንዲጨብጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።

መሰል ሞዴል ትምህርት ቤት መቋቋሙ ለሙያ ትምህርት የሚሰጠውን የተዛባ አስተሳሰብ ለማስተካከል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025