የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው-የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው ሲሉ የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ የተካሄደው የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።


በጉብኝታቸውም ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አስድናቂ የምህንድስና ውጤት መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ አፍሪካ በራሷ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል በማሳየት ትርክት የቀየረ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በልዩ ጽናትና በራሳቸው አቅም ግድቡን ማሳካታቸው ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሰጠና የሚደንቅ ደማቅ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል።


ግድቡ የፅናት፣ የራስን መቻል እና የአህጉራዊ ኩራትና የአንድነት ብርሃን መሆኑንም ተናግረዋል።


ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሕዝባቸውን በማስተባበር ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት መስጠቱንም ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን ሳይሰስቱ ለዓመታት በመትጋት እውን ያደረጉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ በራሷ አቅም ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እንደምታሳካ ህያው ምስክር ነው ብለዋል።


አፍሪካውያን ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም ማከናወን አይችሉም የሚለውን የተዛባ ትርክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሉ ለሙሉ መቀልበሱንም ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ የሕዝቧን የተደመረ አቅም በመጠቀም ብሔራዊ ፕሮጀክቷን እውን አድርጋለች ያሉት የሚዲያ ባለሙያዎቹ ፥ ግድቡ አፍሪካውያን ሲተባበሩ የጋራ ህልማቸውን እውን ማድረግ እንደሚችሉ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል።


የአፍሪካን አቅም፣ ታላቅነትና በልጆቿ ጥረት ግቧን ማሳካት እንደምትችል ህያው ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል።


ግድቡ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ጉልህ አበርክቶ ያለው መሆኑንም የሚዲያ ባለሙያዎቹ ጠቅሰዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዋጋ ከፍለው ያሳኩት አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።


ለመላው አፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነው ሕዳሴ ግድብ በአህጉሪቱ አዲስ የይቻላል የለውጥ ጉዞን ያቀጣጠለ መሆኑን ገልጸዋል።


የበለጸገችና እና አንድነቷ የጠነከረ አፍሪካን እውን በማድረግ ሂደት ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የበርካታ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መመረቁ ይታወሳል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025