የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በጅግጅጋ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሃግብር ውስን ቦታን በመጠቀም ውጤታማ ሆነዋል

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅግጅጋ፤ ህዳር 11/2018 (ኢዜአ)፦ በሌማት ትሩፋት ውስን ቦታን በማልማት የአመጋገብ ሥርዓታቸውን ከማሻሻል ባለፈ የሥራ ባህላቸውን እየለወጡ መሆናቸውን በጅግጅጋ ከተማ የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች ተናገሩ።

የሌማት ትሩፋት መርሃግብር በውስን ቦታ ላይ አትክልትና ፍራፍሬን እንዲሁም እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦን በዘመነ መንገድ በማልማት ማዕዱን ምሉዕ ከማድረግ ባለፈ የአመጋገብ ስርዓቱን ለማሻሻል እንዲያስችል ታስቦ የተተገበረ ነው።

በዚህ መርሃ ግብርም በከተማም ሆነ በገጠሩ የአገሪቷ ክፍሎች በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ በእንስሳትን ተዋጽኦ ስራ ላይ በመሰማራት ከራሳቸው አልፈው ለገበያ ማረጋጋት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸው ታውቋል።

የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎችም በእንስሳት፣ በአትክልትና ፍሬፍሬ እንዲሁም በሌሎች የከተማ ግብርና ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ በመሆን ላይ ይገኛሉ።

በከተማው በዘርፉ ከተሰማሩ ነዋሪዎች መካከል አቶ ከድር ዓሊ አንዱ ሲሆኑ በሌማት ትሩፋት መርሃግብር ባላቸው አነስተኛ መሬት ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።

በጓሮአቸው ያላቸውን ውስን ቦታን በአግባቡ ተጠቅመው የተለያዩ የአትክልት አይነቶች በማምረት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ወይዘሮ ፋጡማ አደን በበኩላቸው በሌማት ትሩፋት መርሃግብር የጓሮ አትክልት በማምረት ቤተሰባቸውን በተሟላ ማዕድ ከመመገብ አልፈው ለገበያ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።

በተለይም ቆስጣ፣ ሰላጣ፣ ቃሪያና ሌሎችንም በማምረት ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸው፤ ሌሎችም ውስን ቦታ ያላቸው ሰዎች የእሳቸውን አርአያ ተከትለው አልምተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መክረዋል።

ከዕለት ሥራቸው ጎን ለጎን በሌማት ትሩፋት መርሃግብር የጓሮ አትክልት በማልማት ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ አቶ አብዲ ቼህ ናቸው።

አቶ አብዲ እንደሚሉት በአቅራቢያ ያሉትን የውሃ አማራጮችን በአግባቡ በመጠቀም ባላቸው ጓሮ ላይ ውጤታማ ስራ መስራት ችለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025