የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የደመወዝ ማሻሻያው የሥራ ተነሳሽነታችንን ይበልጥ አጠናክሮልናል - የመንግስት ሠራተኞች 

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ ፤ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡-መንግስት ያደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የሥራ ተነሳሽነትን ይበልጥ በማጠናከር የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ እንዳበረታታቸው በአምቦ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ተቋማት የመንግስት ሠራተኞች፤ የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ውድነት ጫናን በመቀነስ በቀጣይ ሕዝቡን በላቀ ቁርጠኝነትና ብቃት ለማገልገል ብርታት እንደሆናቸው ገልጸዋል።

የከተማው አስተዳደር ትምህርት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ አቶ ጋዲሳ ደሳለኝ፤ በተደረገላቸው የደመወዝ ማሻሻያ ደስተኛ እንደሆኑ በመግለፅ ይህም የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እንደሚያግዝ ተግረዋል፡፡የሥራ ተነሳሽነታቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ያበረታታቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣትም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የአምቦ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ አቶ ታደሰ ለገሰ በበኩላቸው፤ መንግስት ያደረገው የደመወዝ ማሻሻያ ተገቢ እና ወቅታዊ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል።

ይህም ሕብረተሰቡን በበለጠ ፍጥነትና ጥራት በማስተናገድ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ተነሳሽነታቸው እንዲጨምር እንዳበረታታቸው ገልጸዋል።

የደመወዝ ማሻሻያው የመንግስት ሠራተኞች የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም እንደሚያግዝ የገለጹት ደግሞ የአምቦ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ ወይዘሮ ትእግስት ፈይሳ ናቸው።

ማሻሻያው ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቀንስ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ህገ ወጦች ላይ የተጠናከረ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል።

የአምበ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ከበደ፤ የመንግስት ሠራተኛ የደመወዝ ማሻሻያው በከተማ አስተዳደሩ ተግባራዊ መደረጉን አረጋግጠዋል፡፡

በዚህም ሠራተኛው ደስተኛ መሆኑን አንስተው፤ ለተገልጋዩ ሕብረተሰብ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት እርካታን ለማረጋገጥ መትጋት እንዳለበት አስገንዘበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025