የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለሀገር ያለው ፋይዳ ዘርፈ ብዙ ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለሀገር እድገት መፋጠን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በመላ አገሪቷ ነገ ይጀመራል።

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአዲስ አበባ ስታቲስቲክስ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ተሰማ ኡርጌሳ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የሚገኙ መረጃዎች በዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ፖሊሲዎች እና ስትራቴጂዎች በትክክለኛ ግብዓት ያገለግላሉ።

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ጥናት ጠቃሚ የመረጃ ግብዓት በማስገኘት በኢኮኖሚያዊ ልማት ላይ ያለው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

እንደሥራ አስኪያጁ ገለጻ፤ በአዲስ አበባ ያሉ የንግድ ተቋማት እና ኢንዱስትሪዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያሉባቸውን ችግሮች በመለየት ጥናት በማድረግ ለፖሊሲ ግብዓትነት እንዲውል ለማድረግ ያግዛል ነው ያሉት፡፡

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የቢዝነስ ስታቲስቲክስ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ናቃቸው ነጋሽ በበኩላቸው፥ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በሁሉም ክልሎች ያሉትን ድርጅቶች እና ሁሉንም የኢኮኖሚ አውታሮች ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።

በቆጠራ ስራው ለሚሰማሩ ባለሙያዎች ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፤ ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመላ ሀገሪቷ የቆጠራው የመስክ ስራ እንደሚጀመር ታውቋል፡፡

ሁሉም ዜጎችና የንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰበሰበው መረጃ ለሀገር የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት መረጃውን በመስጠትና በጎ ትብብር በማድረግ እንዲያግዙም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ላለፉት 25 ቀናት በመላ ሀገሪቷ በ56 የስልጠና ማዕከላት ሲሰጥ የቆየው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ስልጠናን አጠናቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025