የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን  ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ  የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ይጠናከራል 

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ማያ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የማያ ከተማ መስተዳደር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

የከተማው መስተዳድር ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዲ ዩያ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ በከተማ መስተዳድሩ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ በሚከናወነው ስራ በየዓመቱ የሚሰበሰበው ገቢ እየጨመረ ነው።

በዚሁ ልክ በሶስቱም ክፍለ ከተሞች ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።

በዘንድሮ በጀት ዓመትም ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ በመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከ658 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።

የገቢ አሰባሰቡ እቅዱን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት በሚቻል መልኩ መከናወኑን የጠቀሱት ሃላፊው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ደግሞ በ271 ሚሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱን አመላክተዋል።

ለገቢው መጨመር የተቀመጡትን የገቢ ርዕሶች በአግባቡ ለመተግበር የተካሄደው የተቀናጀ ጥረትና የግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብርን የመክፈል ግንዛቤ እያደገ መምጣት ተጠቃሽ መሆናቸውን አቶ አብዲ አስረድተዋል።

የክልሉ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በራስ ገቢ ወጪን ለመሸፈን የተጀመረውን ጥረት ለማሳካት ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

የግብር ገቢው በየዓመቱ መጨመር የህዝብ የልማት ተጠቃሚነት እንዲጎለብት እያስቻለ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በከተማ መስተዳድሩ የሚሰበሰበው ገቢ ላይ ተጽዕኖ የሚያስከትለውን የኮንትሮባንድ ንግድ በመከላከል ረገድ የሚከናወነው የተቀናጀ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊ መስመር የማስገባትና ደረሰኝ በማይቆርጡ የንግድ ድርጅቶች ላይም የሚከናወነው የቁጥጥርና ክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025