የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛሉ

Jul 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ስልጠና እየወሰዱ እንደሚገኙ ተገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠናን ሐምሌ 2016 ዓ.ም ማስጀመራቸው ይታወሳል።

ስልጠናው በዋናነት በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ለኢዜአ እንደገለጹት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ወሳኝ ከሆኑ መሰረቶች አንዱ የዲጂታል ስነ-ምህዳሩን ማስፋት መሆኑን አንስተዋል፡፡

የዲጂታል ስነ ምህዳሩን ከሚያሰፉ ስራዎች መካከልም ዋነኛው የክህሎት ግንባታ መሆኑን ገልጸው፤ በዘርፉ እውቀትና ክህሎት ያለው የሰው ሀይል ማፍራት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የኮደርስ ስልጠናው የዜጎችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት በማዳበር እንደሀገር የተጀመረውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

በዚህም እስካሁን ባለው የስልጠናው ሂደት 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች የኮደርስ ስልጠናን እየወሰዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

እስካሁን በኢኒሼቲቩ በተሰራው ስራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስልጠናውን ካጠናቀቁ ወጣቶች መካከል 900ሺህ የሚሆኑት የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ሀገራዊ ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ ክልሎችም የሚጠበቅባቸውን ድርሻ ለመወጣት እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በዚህም የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ መኖራቸውን ነው ስዩም መንገሻ ጨምረው የገለጹት።

የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች በዲጂታል ኢኮኖሚ ላይ ንቁ ተሳታፊ እና አምራች እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን ክህሎት የሚያገኙበት መሆኑንም ገልጸዋል።

በተያዘው ክረምት ወቅትም ተማሪዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በትምህርት ቤቶችና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስልጠናውን በመውሰድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልእክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025