የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የሀገር ውስጥ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትን በጥራትም በስፋትም ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ነው - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትን በጥራትም በስፋትም ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ።

የኮምቦልቻ ተርሚናል በተያዘው በሐምሌ ወር መጨረሻ እንደሚመረቅ ተመላክቷል።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በኢትዮጵያ ትልቁን የአየር ትራንስፖርት የሚሰጠው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይ በ22 ከተሞች የበረራ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በአፍሪካ ትልቅ አገልግሎት መሆኑን ጠቁመዋል።

አገልግሎቱ አሁንም በቂ አለመሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ደረጃውን በጥራትም ሆነ በስፋት ለማሳደግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከእነዚህም መካከል መንገደኞች የሚስተናገዱባቸው ተርሚናሎች ደረጃቸውን የጠበቁ በማድረግ ረገድ በበርካታ ኤርፖርቶች ከፍተኛ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል።


በተጨማሪም የአዳዲስ የተርሚናሎች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው የኮምቦልቻ ተርሚናል ግንባታ ስራም በተያዘው የሐምሌ ወር መጨረሻ እንደሚመረቅ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በሽሬ፣ ነቀምት እና ደምቢዶሎ አዳዲስ ተርሚናሎች ለመገንባት እቅድ መያዙን ጠቁመዋል።

ነባር የአውሮፕላን መንደርደሪያዎችን በማደስ ትልልቅ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ በሚችሉበት ደረጃ ከፍ የማድረግ ስራዎችም እየተሰሩ መሆኑን አመላክተዋል።

ምንም ኤርፖርቶች ባልነበሩባቸው አካባቢዎችም ስድስት ኤርፖርቶች እየተገነቡ መሆናቸውንም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለጹት።

ከእነዚህም መካከል የያቤሎ ኤርፖርት በነሐሴ ወር እንደሚመረቅ ተናግረዋል።


አየር መንገዱ የሀገር ውስጥ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትን በጥራትም ሆነ በስፋት ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025