የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በጎንደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው

Jul 7, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡንም የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸው ተገለጸ።

የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ፣ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ የስራ ሃላፊዎች በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ዋና አፈጉባኤዋ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በጉብኝቱ ላይ እንደተናገሩት፤ በከተማው የሚካሄዱ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተቀናጅቶ የመምራትና ጀምሮም የማጠናቀቅ ተቋማዊ አቅምና የአመራር ቁርጠኝነት የታየበት ነው።


በተለይ የከተማው የኮሪደር ልማት ስራ ሕዝቡን በባለቤትነት በማሳተፍ በአጭር ጊዜ ውስጥ የታየው ለውጥና የተመዘገበው ስኬት በሞዴልነት የሚወሰድ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማት ስራው የከተማውን ውበት የገለጠ ምቹና ውብ የከተሜነት ገጽታን ያላበሰና ለዜጎችም የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።


በተጨማሪም በከተማው እየተካሄደ ያለው የሴፍቲኔት መርሀ ግብር በከተሞች የሚታየውን ድህነት በመቀነስ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች ጥሪት አፍርተው በአጭር ጊዜ ከድህነት የሚወጡበት ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እንደሆነ መገንዘባቸውን ተናግረዋል።


በከተማው እየተገነባ ያለው ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ከህገ ወጥ ደላሎች ነጻ በሆነ መንገድ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ገበያውን በማረጋጋትና የኑሮ ውድነቱን በመቀነስ በኩል የጎላ ፋይዳ እንዳለውም ገልጸዋል።

የጠራ እቅድና ሀሳብን ወደ ተግባር ለመለወጥ የአመራሩና የሕብረተሰቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴና ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አስረድተዋል።

የክልሉ ምክር ቤት ሴቶች ህጻናት ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ አበራሽ ታደሰ በበኩላቸው፤ በከተማው እየተካሄደ የሚገኘው የሴፍቲኔት መርሀግብር የሴቶችን ኑሮና የስራ ባህል የቀየረ የገንዘብ ቁጠባ ባህላቸውንም ያሳደገ ነው ብለዋል።


በከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ለቴክኖሎጂ መስፋፋትና ለወጣቶች የስራ እድል ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሱሌይማን እሸቱ ናቸው።

የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ፤ የተካሄደው ጉብኝት የከተማ አስተዳደሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት እንዲያከናውን በቂ ግብአት የተገኘበት ነው ብለዋል።


በጉብኝቱ የኮሪደር ልማት ስራን ጨምሮ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ፣ የከተማ ሴፍቲኔት ስራዎች ፣ የአረጋውያን የምገባ ማዕከልና የአረንጓዴ አሻራ ዝግጅት ምልከታ የተካሄደ ሲሆን፤ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በጎሃ ተራራ ላይ ተከናውኗል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025