የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው

May 30, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ ፤ግንቦት 20/2017 (ኢዜአ)፡- የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ከጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ጋር በመሆን በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጽህፈት ቤት የተገነባውን የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍል መርቀዋል።


ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የዲጂታል መሰረተ ልማት እንደ ሀገር ለታለመው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የዲጂታል መሰረተ ልማት በተለይም የሰው ኃይል ልማቱን በማሳለጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ዓይነተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂው የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ወጪና ጊዜ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማሳለጥ የሚያስችል ስለመሆኑም አስረድተዋል።

ሚኒስቴሩ ከክልሎች ጋር በመተባበር በዕለቱ የተመረቀውን የዲጂታል ኮሙኒኬሽን ስማርት ክፍል ያስገነባው የክልሎችን ፍትሐዊ ተጠቀሚነት ለማረጋገጥ በማለም መሆኑንም ገልጸዋል።


የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው የዲጂታል መሰረተ ልማት የታለመውን የልማትና የብልጽግና ጉዞ ለማሳለጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

የዲጅታል መሰረተ ልማት እየተካሄዱ ለሚገኙት የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሳለጥ የጎላ አበርክቶ እንዳለው አንስተው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በክልሉ ላስገነባው የስማርት ኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማት አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025