የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ ዕድገቱን ከማሳለጥ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው - ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ ዕድገቱን ከማሳለጥ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ተናገሩ።

20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

በስብሰባው የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

ከስብሰባው ጎን ለጎንም ሀገራት በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ያላቸውን ተሞክሮ የሚለዋወጡበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ አካታች የኢኮኖሚ ሥርዓት በመዘርጋትና በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ ስኬታማ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው።

የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ለስራ ዕድል ፈጠራው ያለውን ጉልህ ሚና በማጤንም መንግሥት የግሉን ዘርፍ በማበረታታት ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጥር ሁኔታዎችን ማመቻቸቱንም ጠቅሰዋል።

ከዚህ ቀደም በአመዛኙ በግብርና ላይ የተመሰረተ የሥራ ዕድል ፈጠራ እንደነበር አስታውሰው፤ የብዝሃ ኢኮኖሚ አሰራርን በመከተል ከግብርና ባሻገር በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እንዲሁም በዲጂታል ኢኮኖሚ የሥራ ዕድል ፈጠራውን የሚያሳልጡ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብርም የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ ኢትዮጵያ ቁልፍ አጀንዳ ማድረጓን ገልጸው፤ ይህም የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴው ላይ አበረታች ውጤቶች እንዲገኙ እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን ለአብነት ጠቅሰው፤ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በግንባታው መስክ የተገኘው ውጤት ተጠቃሽ መሆኑን አስረድተዋል።

በሀገሪቱ ወደ ሥራ የገቡት የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ፈጥረዋል ነው ያሉት።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ደኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በሴፍቲኔት መርሃ ግብር በገጠርና በከተማ የሥራ ዕድል ዜጎች ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።

ክህሎት መር ፖሊሲ አሰራርን በመተግበርም የተቋማት ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የሰለጠነ የሰው ኃይል ወደ ሥራ እንዲገባ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ፍሬ እያፈሩ መሆኑንም አንስተዋል።

በተለይም በዲጂታል መስክ ስታርታፖችን በመደገፍ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ በተዘረጋው ማበረታቻ ሥርዓት በርካታ ስታርታፖች ምህዳሩን እየተቀላቀሉ ነው ብለዋል።

በክህሎት ልማት ዘርፍ ቀጣናዊ ትብብሮችን በማጠናከር ለጋራ ብልጽግና ትኩረት ተሰጥቷል ሲሉም ተናግረዋል።

በዓለም የሥራ ድርጅት የልማትና ኢንቨስትመንት ቅርንጫፍ የቅጥር ፖሊሲ መምሪያ ኃላፊ ሚቶ ቱስካማቶ እንዳሉት፤ እያደገ የመጣው የመሰረተ ልማት ግንባታ ተገቢው የሥራ ዕድል እንዲፈጥር ሀገራት የተሻለ አሰራር ቀርጸው ሊንቀሳቀሱ ይገባል።

በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ በተለይም ተጋላጭ የሆኑ የኀብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ላይ ርብርብ ይጠይቃል ነው ያሉት።

ስብሰባውን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከዓለም የሥራ ድርጅት(ILO) ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን፤ ከግንቦት 11 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025