የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ዘርፉን በሳይንሳዊ ምርምርና በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመደገፍ ማዘመን ይገባል

May 15, 2025

IDOPRESS

ጂንካ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀገራዊ ጥቅም ለማሳደግ በሳይንሳዊ ምርምር ማጎልበትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመደገፍ ማዘመን እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።

በጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በቱሪዝም ላይ ያተኮረ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ ተካሂዷል።

በኮንፍረንሱ የምርምር ስራዎቻቸውን ያቀረቡ የዘርፉ ተመራማሪዎች ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀገራዊ ጥቅም ለማሳደግ በሳይንሳዊ ምርምር ማጎልበትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት መደገፍ ይገባል ብለዋል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህል ተመራማሪ ፕሮፌሰር ይስሃቅ ከቸሮ ቱሪዝምን በምርምርና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዘመን በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሑፍ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ በቱሪዝም ሀብቷ ከፍተኛ አቅም ያላት ብትሆንም ከዘርፉ የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያገኘች አለመሆኑን ጠቁመዋል።

እንደ ኬኒያ ያሉ ሀገራት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ከቱሪዝም ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ያሉት ተመራማሪው፤ ኢትዮጵያም ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ለማግኘት የምርምር ውጤቶችን ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር በማቀናጀት መጠቀም እንዳለባት አመልክተዋል።


የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ተወካይ አቶ ኢብራሂም ጀማል በበኩላቸው፤ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማነቃቃትና ለማዘመን ሳይንሳዊ ምርምሮች ትልቅ ጠቀሜታ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ቱሪዝም የዩኒቨርሲቲው ዋነኛ የትኩረት መስክ እንደሆነ ገልጸው፥ ዘርፉን በሳይንሳዊ ምርምር በማጎልበት ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀብት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይኒቱ መልኩ በበኩላቸው፥ በክልሉ ያሉ በርካታ የቱሪስት መስህቦችን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025