የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በሀገሪቱ ባለው እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የግል ባለሃብቱ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ መጎልበት ይኖርበታል

May 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2017(ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ ባለው እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የግል ባለሃብቱ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ መጎልበት እንዳለበት የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

በኢትዮጵያ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ባሉ እምቅ የኢንቨስትመንት አማራጮች የግል ባለሀብቱ በስፋት ቢሰማራ ተጠቃሚ እንደሚሆንም ነው ሚኒስቴሩ ያመላከተው፡፡


ግብርና ሚኒስቴር ከዓለም አቀፍ እንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩትና ከዓለም ዓቀፍ የግብርና ጥናት አማካሪ ግሩፕ ጋር በመቀናጀት በኢትዮጵያ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ መጽሐፍን የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ እንዳሉት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ባለቤት ነች፡፡

የእንስሳትና ዓሳ ሃብት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማስፋት፣ ለግብርና ስራና ለኢንቨስትመንት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝም አመላክተዋል፡፡

በሀገሪቱ እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ቢኖርም ከዘርፉ የሚገኘው ጥቅም አነስተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ይህን ለማሳደግ የግል ባለሃብቱ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ መጎልበት እንዳለበት ነው የገለጹት።

በኢትዮጵያ በእንስሳትና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ያለውን የኢንቨስትመንት አቅምና አማራጮችን ላይ ያተኮረ መጽሐፍ መዘጋጀቱ የባለሃብቱን ግንዛቤ ለማጎልበት እንደሚያግዝም ተናግረዋል።

በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ኢንቨስትመንትና ምርት ግብይት ዴስክ ኃላፊ ከድር ሉባንጎ በበከላቸው፤ መጽሐፉ ኢትዮጵያ በመኖ ምርት፣ በማር፣ በዓሳ እና በተለያዩ እንስሳት ሀብቶች ያላትን ፀጋዎች በሙሉ ያካተተ ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የሆለታ ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ ተመራማሪ ዶክተር ተመስገን ጀምበር፤ በመጽሐፉ ዝግጅት ላይ መሳተፋቸውን ገልጸው፤ በመጽሐፉ ውስጥ የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር ለኢትዮጵያ በሚመች መልኩ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ያለው የእንስሳት ምርትና እርባታ በአርሶና አርብቶ አደሩ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አስታውሰው፤ መጽሐፉ ባለሀብቶች በዘርፉ ባሉ ምቹ ዕድሎች ዙሪያ መረጃዎችን እንዲያገኙና እንዲሳተፉ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ስጋ አምራችና ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ከሊፋ ሁሴን በበኩላቸው የማህበሩ አባላቶች ስጋን ወደ ውጭ በመላክ ሀገሪቱ ከስጋ ምርት ማግኘት የሚገባትን የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሆኖም ግን አልፎ አልፎ እንስሳት አቅርቦት ችግር መኖሩን ጠቅሰው አሁን የተዘጋጀው መጽሐፍ በዘርፉ ያሉትን ክፍተቶች በመፍታት በኩል አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

እንደ ግልም ሆነ እንደ ማህበር በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለመሰማራት ማቀዳቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025