የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በምዕራብ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል

May 7, 2025

IDOPRESS

ጊምቢ፤ሚያዝያ 28/2017 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ገለጸ።


የምዕራብ ወለጋ ዞን ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገረመው ታደሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 2 ቢሊዮን 751 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።


የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለውም ገልጸዋል።


በዞኑ የሰፈነው ሰላም በተለይም ለንግዱ ማህብረሰብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ ነጋዴው ግብሩን በአግባቡ እንዲከፍል ማስቻሉ ደግሞ ገቢው በዚህ ልክ ለመሰብሰቡ እንደዋነኛ ምክንያት ጠቅሰዋል።


እንዲሁም የጽህፈት ቤቱ ሠራተኞችና አመራሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ ባደረጉት ቅንጅታዊ ጥረት ገቢው ሊሰበሰብ መቻሉን ተናግረዋል።


የንግዱ ማህበረሰብ የግብርና የታክስ ሕጎችን ተረድተው ግብራቸውን በጊዜ መክፈል እንዲችሉ በጽሕፈት ቤታቸዉ በተለያዩ ጊዜያት ስልጠናና የውይይት መድረኮች መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።


በተለይም በተያዘው በጀት ዓመት ግብር ከፋዮች በጊዜ እንዲስተናገዱ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ስርዓት መዘርጋቱን ሃላፊው አስረድተዋል።


የመንግስትን ታክስና ግብር በጊዜና በታማኝነት መክፈል የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ ያስችላል።


በመሆኑም ሁሉም ግብሩን በወቅቱና በታማኝነት በመክፍል የድርሻውን እንዲወጣ አቶ ገረመው አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025