የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

አዲሱ የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲ ምርታማነትን በማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዚያ 15/ 2017/(ኢዜአ)፦አዲሱ የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲ ፖሊሲ ምርታማነትን በማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ገለጸ።


በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ኃላፊ እያሱ አብርሃ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት በፖሊሲው ዙሪያ ለግብርና ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት ተከታታይ ስልጠና እየተሰጠ ነው።


ከዚህ ቀደምም 1 ሺህ 500 ለሚሆኑ የግብርና ባለሙያዎች በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል።


አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በዋናነት የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ዓላማ ያለው በመሆኑ ፖሊሲው በክልሉ ተፈፃሚ እንዲሆን እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል።


በክልሉ ያሉ የግብርና ባለሙያዎች እና የግል ባለሃብቶችን ጨምሮ ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት አዲሱን ፖሊሲ አውቀው እንዲያስፈፅሙ የተጀመረው ስልጠና ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።


ከፖሊሲው ቁልፍ መስኮች መካከል ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እና የገጠር መዋቅራዊ ሽግግርን ማረጋገጥ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ግብርናውን በማዘመን የግል ባለሃብቱን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ መሰረታዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ተናግረዋል።


የግብርና ሚኒስቴርም በክልሉ ለዘርፉ እድገት እውን መሆን የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ገልፀው፥ ለዚህም ቢሮው የላቀ ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።


በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ላዕላይ ቆራሮ ወረዳ የእርሻ ጽህፈት ቤት የግብርና ባለሙያ ወይዘሮ ምብራቅ ገብረመድህን በፖሊሲው ቁልፍ ስትራቴጂ ዙሪያ ስልጠና መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡


ስልጠናው ተጨማሪ አቅምና ግንዛቤ ይዘን በሙያችን አርሶ አደሩን ለመደገፍ ያግዘናል ብለዋል፡፡


ለአርሶ አደሩ የሚሰጡትን ሙያዊ ድጋፍ ለማሳደግ በፖሊሲውና ስትራቴጂው ዙሪያ ተከታታይ ስልጠና መሰጠቱ አስፈላጊ እንደሆነ የገለፁት ደግሞ የዚሁ ወረዳ የግብርና ባለሙያ አቶ ተክላይ ሞገስ ናቸው፡፡


በግብርና ስራ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣትና በተለይ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ሙያዊ ኃላፊነታችንን ለመወጣት የሚያስችለንን የአቅም ግንባታ ስልጠና ወስደናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025