የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

አፍሪካውያን ዓለም አቀፍ ጫናዎችን መቋቋም የሚያስችል አቅም መገንባት ይኖርብናል - የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2017(ኢዜአ)፦አፍሪካውያን ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ለመቋቋም የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አቅም መገንባት ይኖርብናል ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ።


የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት 24ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ በአዲስ አበባ ማካሄድ ጀምሯል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት የአንድ አባል ምርጫ ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል።


በተመሳሳይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የዓለም አቀፍ ህግ አማካሪ አደረጃጀት (AUCIL) አንድ አባል እንዲሁም የአፍሪካ የህዋ ምክር ቤት (AfSC) አንድ አባል ምርጫ ይከናወናል ።


በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪ እና ማዕድን ኮሚሽን እና የትምህርት ፣ሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር የምርጫ ሂደት አስመልክቶ የተዘጋጀ ረቂቅ ሪፖርት ያዳምጣል።


የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የአፍሪካ አህጉር በርካታ ውስብስብ ችግሮች እየገጠሙት ይገኛል።

የአንዳንድ እርዳታ ሰጭ ተቋማት ድጋፍ መቋረጥ በጤናና በምግብ ዋስትና ላይ ተግዳሮት መፍጠሩን ጠቅሰው፤ አፍሪካውያን ዓለም አቀፍ ጫናዎችን መቋቋም የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የመሳሰሉ ዘዴዎችን ለመተግበር በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።

የአንጎላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የወቅቱ የምክር ቤቱ ሊቀ-መንበር ቴቴ አንቶኒዮ በበኩላቸው፤ ሰላም እና መረጋጋት ለእድገት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

አህጉራዊ ተቋማት የሰላም እና የጸጥታ ጉዳዮችን ለመቋቋም የሚያስችል ጠቃሚ ግብዓት እንዳላቸው ጠቁመው፤ ይህም የውሳኔ ሰጭውን አካል መፍትሄ የሚፈለግ መሆኑን ተናግረዋል።

የአፍሪካ ህብረት እነዚህን ተግዳሮቶች በጥበብ እና አርቆ አስተዋይ አመራር በመምራት ረገድ ንቁ መሆን አለበት ያሉት ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተወካይ አምባሳደር ሒሩት ዘመነ ናቸው።

የ2063 አጀንዳን ራዕይ ለማሳካትና የበለፀገች አህጉርን ለመፍጠር አህጉራዊ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ቀልጣፋ ስራ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብስባ እየተካሄደ ያለው በየካቲት 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተደረገው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በተላለፈው ውሳኔ መሰረት ነው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025