የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኮሪደር ልማቱ መንገዶችን ለሚፈለገው ተግባር በማዋል በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Apr 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማቱ መንገዶች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውሉ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገልጿል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች በአዲስ አበባ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የኮሪደር ልማቶችን፣ ብሔራዊ ቤተ-መንግስትንና አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡


በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴዔታ አማካሪ ቶሎሳ ፉፋ(ዶ/ር) ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወኑ መሰረተ ልማቶች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው።

በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ በመቀየርና ዘመናዊ አኗኗርን በማስረጽ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ያደረጉት ጉብኝትም በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ለመመልከት እድል የፈጠረ ነው ብለዋል።

በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የመንግስትን የመፈጸም አቅምና ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ከመሆናቸው ባሻገር ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጉልህ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆናቸውን አንስተዋል።

በጉብኝቱ የተመለከቷቸው ፕሮጀክቶች በአጭር ግዜ ውስጥ ግንባታቸው ተጠናቆ አገልገሎት መስጠት የጀመሩ መሆናቸው ደግሞ በእጅጉ የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በከተማዋ የኮሪደር ልማት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የተገነባ መሆኑ ለትራንስፖርት ዘርፉ ያለው ፋይዳ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል።


በዋናነት የኮሪደር ልማቱ መንገዶች ለታለመላቸው ዓላማ በማዋል ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስትራቴጂ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025