የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ድጋፍ ያደርጋል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ስራዎች ድጋፍ ለማድረግ እንደሚሻ አስታወቀ።


የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)፥የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎችን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።


በኩታ-ገጠም የግብርና ልማት ስራዎችን ማስፋፋት፣ በግብርናው ዘርፍ የስራ ዕድል ፈጠራን ማስፋትና ዘርፉን በቴክኖሎጂ በመደገፍ እንዲዘምንና ሳቢ እንዲሆን በማድረግ ወጣቶችን ወደ ዘርፉ እንዲገቡ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።


እንዲሁም በግብርና ኢንቨስትመንት፣በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት እና በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎች ምርታማነትን ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።


ሚኒስትሩ የግብርና ዘርፍ ስራን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን መንግስት ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረ አመልክተዋል።


የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025