የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የህንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ መሰማራት እንደሚፈልጉ ገለጹ

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦የህንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ ።


በህንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋው ከህንዱ ፒኤችዲ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት እና ኬኤልጂ ግሩፕ ኦፍ ኢንዱስትሪስ ከተሰኘው አምራች ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሽሪ ሄርማንት ጃን ጋር ተወያይተዋል።


ውይይቱ የኢትዮጵያ እና ህንድ የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነው።


አምባሳደር ሞላልኝ የኢትዮጵያን ብዝሃ የኢንቨስትመንት እድሎች አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።


የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ያሉ አማራጮችን እንዲቃኝ ጥሪ አቅርበዋል።


ሽሪ ሄርማንት ጃን በምክር ቤቱ ስር ያሉ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸው እ.አ.አ ጁን 2025 የንግድ ልዑክ በኢትዮጵያ ጉብኝት እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።


ከ130 ሺህ በላይ አባላት ያሉት ፒኤችዲ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የህንድ ላኪዎችን የሚወክል ግዙፍ ተቋም መሆኑን በኒው ዴልሂ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።


ኬኤልጂ ግሩፕ ኦፍ ኢንዱስትሪስ በህንድ እና እስያ ግዙፍ የፕላስቲክ እና የፕላስቲክ ውጤቶች አምራች ኩባንያ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025