የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ሴቶች በሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ የግንባር ቀደምትነት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፦ ሴቶች በሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ የግንባር ቀደምትነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሴቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማህበር (SEWIST) 6ኛ ዓመታዊ ጉባኤ ተካሂዷል።


ጉባኤው የተካሄደው "የወደፊቱን የሚመሩ ሴቶች፤ የሴት ተመራማሪዎችን በሳይንስ፣በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ማብቃት" በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

የማህበሩ ጉባዔ ሴቶችን በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ ፣ፈጠራና ምርምር እድገት ያላቸው ሚና፣ ያሉ እድሎች እና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ ነው።

ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ሴቶች በሳይንሳዊ ግኝቶች፣ በቴክኖሎጂ እድገት እና በፈጠራ መፍትሄዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊወጡ ይገባል።

በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ /STEM/ ዘርፎች የሴት ምሁራን ሚና ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መፍትሄ ለማምጣት ሴቶችን ያሳተፈ ስራ ማከናወን እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል።

ማህበሩ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና የምርምር ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ሴቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማህበር ፕሬዝዳንት ሄለን ንጉሤ(ዶ/ር ) ኢትዮጵያ በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን በርካታ ስራዎች እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

በዘርፎቹ የተሟላ ውጤት ለማምጣት የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሒሳብ /STEM/ ዘርፎች ያላቸውን አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ሴቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ ማህበር በ2014 ዓ.ም የተቋቋመ እና በሳይንስ ፣ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ሚኒስቴሩ በመረጃው አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025