የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ቀርቧል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ የካቲት 26/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በተለይም የወጭና ገቢ ምርቶችን ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በብዛትና በጥራት ለውጭ ገበያ እየቀረቡ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት፤ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡ ተገልጿል።

በአማራ ክልል የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ዳይሬክተር፤ አቶ ልንገረው አበሻ፤ በበጀት ዓመቱ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ ግብ መያዙን አስታውሰዋል።

በዚህም መሰረት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ቀርቦ ከ215 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።

ለውጭ ገበያ ከቀረቡት ምርቶች መካከልም የሰሊጥ፣ የማሾ፣ የአኩሪ አተርና የቦሎቄ ምርቶች መሆናቸውን ዘርዝረዋል።

ከገበሬው እስከ ገበያ መዳረሻዎች ጥራቱን በጠበቀ አግባብ ተመርቶ ለገበያ እንዲቀርብ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት ማምጣቱንም ተናግረዋል።

በባለፈው በጀት ዓመት ከክልሉ በምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ከቀረበ 3 ሚሊዮን 910 ሺህ ኩንታል የቅባት እህል 478 ሚሊዮን ዶላር መገኘቱም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025