የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ የመስራት ፍላጎት እያሳዩ ነው - አቶ መስፍን ጣሰው</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፡- በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ በጋራ የመስራት ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን የኢትዮያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገለጹ።

አየር መንገዱ በየጊዜው ዓለም አቀፍ አድማሱን በማስፋት ላይ መሆኑንም ተናግረዋል።

የአፍሪካ አህጉርን ደግሞ በአየር ትራንስፖርት የማስተሳሰር ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት፡፡

በአሁኑ ወቅትም በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ከአየር መንገዱ ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎቶች እያሳዩ መሆኑን ገልጸዋል።

በቅርቡ የናይጄሪያ የአቪዬሽንና የኤሮስፔስ ልማት ሚኒስትር አየር መንገዱን መጎብኘታቸውንና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ናይጄሪያ የሚያደርጋቸውን በረራዎች ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ተናግረዋል።

ይህም ለአየር መንገዱም ሆነ ለናይጄሪያውያን መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር መሆኑ ነው ዋና ስራ አስፈጻሚው የገለጹት።


በቀጣይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ አህጉርን በአየር ትራንስፖርት ለማስተሳሰር የጀመረውን ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ለመታደም አዲስ አበባ የመጡ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ከፍተኛ ኃላፊዎች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችሉ ፍሬያማ ውይይቶች መድረጋቸውንም አውስተዋል።

በዚህም ሀገራቱ አየር መንገዶቻቸውን ለማሳደግና አየር መንገድ የሌላቸው ሀገራት ደግሞ ማቋቋም በሚቻልባቸው ሂደቶች ላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በአህጉሪቱ ከ66 በላይ ከተሞች ይበራል።

ይህም የቱሪዝም፣ የንግድ፣ የሰዎች እንቅስቃሴን በማሳለጥ፣ በምጣኔ ሃብት፣ በማህበራዊና በዲፕሎማሲ መስክ የሀገራቱን ትብብርና ተጠቃሚነት በማሳደግ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025