የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>አዋጁ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ለአምራችና አስመራች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበጃል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርና ምርት አምራችና አስመራች ግንኙነት አዋጅ የግብርና ምርታማነትን የሚጨመርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተገለፀ።

የግብርና ምርት አምራችና አስመራች ግንኙነትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ስልጠና በባህር ዳር ከተማ እየተሰጠ ነው።


የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አጀበ ስንሻው እንዳሉት የአምራቶችና አስመራቾች መስተጋብር ለግብርና ምርታማነት ዕድገት ይበጃል።

አዋጁ አምራቹ የሰብል ግብዓት፣ ቴክኖሎጂና ስልጠና ከአስመራች እንዲያገኝ ብሎም ምርቱን በቀጥታ ለአስመራች እንዲያስረክብ ያግዘዋል ብለዋል።

አስመራች ደግሞ ያስመረተውን ምርት በቀጥታ ተቀብሎ ለኢንዱስትሪም ሆነ ለውጭ ገበያ እንዲያቀርብ ዕድል ይሰጠዋል ነው ያሉት።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር አስተዋጽዖ ያላቸው ሁለት ረቂቅ አዋጆችን አጸደቀ

በዚህም አዋጁ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ሁለቱን ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ለትግበራው በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም፤ አዋጁ አምራቾችና አስመራቾች ውል ገብተው ለጋራ ተጠቃሚነትን የሚሰሩበትና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አሻራቸውን እንዲያሳርፉ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።


የክልሉ ህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ባለስልጣን የግብዓትና ግብይት ዳይሬክተር አቶ አለምዘውድ ስሜነህ በበኩላቸው አዋጁ ጥራትና ብዛት ያለው ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ አምራችና አስመራች ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ የሚያስችል አዋጅ ተግባራዊ ሊደረግ ነው

ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከክልል እስከ ወረዳ ባለው መዋቅር የባለድርሻ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025