የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ያለውን ድርድር ለማጠናቀቅ በቂ ዝግጅት አድርጋለች -ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ያለውን ድርድር ለማጠናቀቅ የሚያስችል በቂ ዝግጅት ማድረጓን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሣሁን ጎፌ (ዶ/ር) ጨምሮ የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት ተደራዳሪ ኮሚቴ አባላት ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ጋር ተወያይተዋል።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ውይይቱን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።


በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን የሚደረገውን የድርድር ሂደት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ይዛ እየሰራች መሆኑን በተመለከተ ከዋና ዳይሬክተሯ ጋር ውይይት መደረጉን ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ከ23 ዓመት በፊት ድርድር መጀመሩን አስታውሰው፥ እስካሁን አራት የሥራ ላይ ቡድን ውይይቶች ማካሄዷን ተናግረዋል።


የፊታችን መጋቢት በጄኔቫ ለሚደረገው አምስተኛው የሥራ ላይ ቡድን ስብሰባም በቂ ዝግጅት ማድረጓን ተናግረዋል።


በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ ሀገራት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ መሰጠቱን ጠቁመው፥ 18 አንቀጾች ተዘጋጅተው መቅረባቸውንም ገልጸዋል።


አሁን ላይ ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከዓለም ንግድ ድርጅት ጋር ድርድር ለማጠናቀቅ የሚያስችል በቂ ዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።


የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ማረጋገጣቸውን ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025