የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ለባሕር ዳር ከተማ ኢንቨስትመንት መጎልበት ባለሀብቱ ሚናውን ሊወጣ ይገባል</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ ባሕር ዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ባለሀብቶች በሰላም ማስጠበቅ እና ልማት ላይ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ የከተማዋ አስተዳደሩ ጥሪ አቀረበ።

በባሕር ዳር ከተማ ልማትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።

የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፤ ከተማ አስተዳደሩ ከወትሮው በተለዬ ከተማዋን ለማልማት እየሰራ ነው።

በዚህም የከተማዋን ሰላምና ነዋሪዎችን ደህንነት ከማረጋገጥ በተጓዳኝ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እየተቀላጠፉ ነው ብለዋል።

ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ ስማርት ሲቲ፣ የዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።

ትውልድ ተሻጋሪ ፋይዳ ያለው የከተማዋ ኮሪደር ልማትም ዘላቂና ምቹ የኑሮና የስራ ከተማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑንም እንዲሁ።

ሁሉን አቀፍ የከተማ ልማት ጥረቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ባለሃብቱ የሚጠበቅበትን ወሳኝ ሚና በመረዳት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።

ከተሳታፊ ባለሃብቶች መካከል አቶ እንግዳው ወርቁና አቶ ማስተዋል አያልነህ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ ምቹና ዘመናዊ ከተማ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አድንቀዋል።

በመሆኑም የመንግስትን ጥረት በመደገፍ ከተማን ለኢንቨስመንት ተወዳዳሪ እንድትሆን በባለቤትነት ስሜት እንደሚደግፉ አረጋግጠዋል።

በከተማዋ የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችን መገብኘታቸውን ገልጸው፤ የልማት ስራዎችን ከመጠበቅና ከመንከባከብ ባሻገር አዳዲስ የልማት ስራዎችን በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025