የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ምክር ቤቱ የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 6 /2017(ኢዜአ)፡-የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ።

6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።

በዚሁ ጊዜ የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ የቀረበ ሲሆን የምክር ቤቱ አባላት በአዋጁ ላይ ያላቸውን ጥያቄ እና አስተያየት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጅጌ(ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ በኢትዮጵያ ከሚመነጨው ሀብት አኳያ የሚሰበሰበው ገቢ በቂ አለመሆኑን ገልጸዋል።

በታክስ የሚሰበሰበው ገቢ ለጥቅል አገራዊ ምርት (ጂ ዲ ፒ) ያለው አስተዋጽኦ ከ7 በመቶ እንደማይበልጥ ጠቅሰው ይህም ከሳሃራ በታች ካሉ ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

ገቢ የመሰብሰብ አቅም ሊያድግ እንደሚገባ የገለጹት ሚኒስትሩ አዋጁ ታክስ የመሰብሰብ አቅምን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።

አዋጁ የታክስ መሰረትን ለማስፋት፣ የመንግሥት መሰረተ ልማት አቅርቦት አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር አጋዥ መሆኑን አመላክተዋል።

አንገብጋቢ ለሆኑ የሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የገቢ አቅምን ማሳደግ ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ ለዚህም የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጁ ሥራ ላይ መዋል የላቀ ፋይዳ አለው ብለዋል።

ምክር ቤቱ በንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጁ ዙሪያ በቀረቡ ጥያቄና አስተያየቶች ላይ ከተወያየ በኋላ አዋጁን መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025