የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የካፒታል ገበያ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ እንድትሆን ያስችላታል - የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- የካፒታል ገበያ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ እንድትሆን ያስችላታል ሲሉ የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ትናንት በይፋ አስጀምረዋል፡፡


የናይጄርያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ሥራ አስፈፃሚ ተሚ ፖፖላ በመርሀ ግብሩ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በአፍሪካ ገበያ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

በናይጄርያ ከ62 አመት በፊት የተጀመረው የካፒታል ገበያ በተወሰነ ዘርፍ ላይ ከማተኮር ወጥቶ አማራጭ ገበያ እያፈላለገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ድርሻ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ዘርፉ ሁሉንም በንቃት በማሳተፍ ምርትና አገልግሎቶችን በስፋት ማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ምቹ ፖሊሲዎችና አሰራሮችን በመዘርጋት ለመሰረተ ልማት ማስፋፊያ የሚሆን ገቢ መሰበሰብ የግሉ ዘርፍ ደግሞ የተፈጠረለትን እድል በመጠቀም ገበያውን በስፋት መቀላቀል አለበት ብለዋል፡፡

በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለው ትብብር መጎልበት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቋቋም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያስቀጥል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዓለም ላይ ያለ የካፒታል ገበያ ውጤታማ ኢኮኖሚ መገንባት አስቸጋሪ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ስኬት ላይ ለመድረስ የሌሎች ሀገራትን ልምድ መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡


የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለሥራ እድል ፈጠራ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ገንቢ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡

በመሆኑም ገበያው ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ መሆን የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥርላት እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025